
የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል የሚተጉ በጎ ፈቃደኞች
ልጆች በክረምት ትምህርታቸውን እንዲያሻሽሉ በበጎ ፈቃደኝነት የተነሳሱ ተማሪዎችን በማስጠናት ተግባር እየደረጉ ነው። የማጠከሪያ ትምህርቱ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ለመግባት ተማሪያዎች የሚደርጉትን ጥረት የማገዝ ዓላማ ይዟል።

Loading…

Hosted by Unknown Host · AM · 13 episodes
Established thought leaders with verified media credentials.
News, Analysis and Service from Germany and Europe - in 30 Languages
Unknown Host hosts DW | Amharic - News, a general show with 13 episodes published.

ልጆች በክረምት ትምህርታቸውን እንዲያሻሽሉ በበጎ ፈቃደኝነት የተነሳሱ ተማሪዎችን በማስጠናት ተግባር እየደረጉ ነው። የማጠከሪያ ትምህርቱ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ለመግባት ተማሪያዎች የሚደርጉትን ጥረት የማገዝ ዓላማ ይዟል።

ኢትዮጵያ ያስጠለለቻቸውን ስደተኞች ተጠቃሚ ያደርጋል የተባለው"ማካተት" የተባለው ፍኖተ- ካርታ በተለይ በጋምቤላ ክልል ለሚኖሩ ስደተኞችና ተቀባይ ማኅበረሰቦች በጎ የፖሊሲ አቅጣጫ መሆኑን የቀድሞ የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ተናገሩ። ፍኖተ-ካርታው በዓለምአቀፍ የስደተኞች አስተዳደር ሕግ መሠረት ከተተገበረ አልፎ አልፎ የሚታየውን ግጭት ይቀንሳል ብለዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ተላላፊና ተላላፊ ላልሆኑ በሽታዎች የምርመራና የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል የተባለ ተንቀሳቃሽ የተቀናጀ ማህበረሰብ አቀፍ የጤና ፕሮግራም እየተካሄደ ነው። በፕሮግራሙ የወባ በሽታ መከላከያና የሳንባ በሽታን ጨምሮ ለሰባት አይነት በሽታዎች የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ይሆናል።

ኢትዮጵያ ያስጠለለቻቸው ስደተኞችን ተጠቃሚ ያደርጋል የተባለ"ማካተት" ፍኖተ- ካርታ፤ በተለይ በጋምቤላ ክልል ለሚኖሩ ስደተኞችና ተቀባይ ማኅበረሰቦች በጎ የፖሊሲ አቅጣጫ መሆኑን የቀድሞ የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ተናገሩ። ፍኖተ-ካርታው በዓለም አቀፍ የስደተኞች አስተዳደር ሕግ መሠረት ከተተገበረ አልፎ አልፎ የሚታየውን ግጭት ይቀንሳል ተብሏል።

በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ነው ያለውን እልቂት እና የእርስ በርስ ጦርነት እንዲቆም፣ የኢትዮጵያውያን ትብብር ንቅናቄ ጥሪ አቀረበ። ንቅናቄው ሰሞኑን ባካሄደው ጉባኤ፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ አንድ ገለልተኛ ኮሚሽን በማቋቋም ጉዳዩ እንዲጣራ በማድረግ፣ አጥፊዎች በሕግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እንዲያደርግ ጠይቋል።

በትግራይ ክልል በተለይ መቀሌ ውስጥ ተከታታይ ስብሰባዎች እየተደረጉ ነው። በስብሰባዎቹ የሚደመጡት መልዕክቶች ህወሓት ከኢትዮጵያ ፌዴራል መንግሥት ጋር ያለው ግንኙነት እየተካረረ ለመሄዱን ጉልህ ማሳያ ተደርጓል። የፌዴራል መንግሥት የሚቆጣጠራቸው መገናኛ ብዙኃን፣ ህወሓትን እና መሪዎቹን የሚነቅፉ ተከታታይ ዝግጅቶችን እያስተጋቡ ይገኛሉ።

ጎተ-የባህል ተቋም አዲስ አበባ በጎርጎረሳዉያኑ 1962 ዓ.ም ተመሰረተ። ተቋሙን መርቀዉ የከፈቱት ንጉሠ ነገሥት አጼ ኃይለ ሥላሴ እና የወቅቱ የጀርመን አምባሳደር ፓውለስ ቮን ስቶልዝማን ናቸዉ። ኢትዮጵያ የሚገኘዉ የጀርመኑ የባህል ተቋም የጎተ 64 ኛ ዓመቱን ይዟል። ተቋሙ በሚቀጥለዉ ዓመት 65 ኛ ዓመቱን ለማክበር በዝግጅት ላይ ነዉ።

በደቡብ አፍሪቃ በዉጭ አፍሪቃዉያን ዜጎች ላይ የሚፈፀመዉ ጥቃት እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ ወደ ሃገራቸዉ የሚመለሱ አፍሪቃዉያን ቁጥር እየጨመረ ነዉ። በደቡብ አፍሪቃ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን አብዛኞቹ ሱቆቻቸዉ ተዘርፈዉባቸዋል ፤ ወድመዉባቸዋል፤ አልያም ከሱቃቸዉ ተባረዋል። በርካታ ኢትዮጵያዉያን በየእለቱ ወደ ሃገራቸዉ እየተመለሱ ነዉ።

በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ በሚገኘው አባይ ገዳመ አስቄጤስ አቡነ አረጋዊና ቅድስት አርሴማ አንድነት ገዳም ላይ ሐምሌ 15 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ተፈፀመ በተባለ የድሮን ጥቃት የ2 መነኮሳይት ሕይወት ወዲያው ሲያልፍ፣ በ11 መነኮሳይት ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ አካል ጉዳት መድረሱን የገዳሙ አበምኔትና የወረዳዉ ቤተክህነት ኃላፊ ገለፁ።

ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስትን እንደሥጋት ተመልክተው ከሚወጉ አካላት ጋር ትብብር መፍጠሩን ዐሳውቋል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ላለፉት ስምንት ዓመታት ግድም አገሪቱን የሚመራውን መንግስት ያለማቋረጥ በመውጋት ላይ የነበረው የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነግ-ኦነሰ) ይህን የህወሓት መግለጫን አላስተባበለም፡

የአሜሪካ ሕግ አውጪ ምክር ቤት (ኮንግረስ) አባላት፣ የውጭ ፖሊሲ ጉዳይ ፖሊሲ ባለሙያዎች፣ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች እና ተሟጋቾች የኢትዩጵያን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ሰሞኑን የምስክርነት ቃል መከታተላቸውን ፣የኢትዮጵያ አሜሪካውያን ሲቪል ድርጅቶች ሰብሳቢ አቶ መስፍን መኮንን ለዶቼ ቬለ ዐሳውዋል።

የአገራዊ ምክክር ጉባኤ ተሳታፊዎች በምክክሩ ላይ በሚያቀርቡት ሐሳብ እንዳይጠየቁ ኃላፊነት እንደሚወስድ የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ ተናገሩ። ዋና ኮሚሽነሩ ይህንን ያሉት፦ ከተጀመረ ስምንተኛ ቀኑን በያዘው ጉባኤ ያለፉት ሦስት ቀናት ሂደት ምን እንደሚመስል ዛሬ ቀትር ላይ በሰጡት አጭር ገለፃ ነው።

የአሜሪካው የጠፈር ምርምር ጣቢያ ናሳ፤ ወደ መሬት ሊወድቅ ተቃርቧል የተባለን ቴሌስኮፕ ቀልቦ የሚይዝ ሊንክ የተባለ በሮቦት የታገዘ መንኮራኩር ሰሞኑን ወደ ህዋ አምጥቋል። ይወድቃል የተባለው ስዊፍት የምልከታ ቴሌስኮፕ ከጎርጎሪያኑ 2004 ዓ/ም ጀምሮ በአፅናፈዓለም (Universe ) ከፍተኛ ፍንዳታዎች ከመከሰታቸው በፊት የሚመረምር ነው።

የወይንሸት መጠለያ ካምፕ ነዋሪ አቶ መካሻ ይመር ለሁለት ወር ከ10 ቀናት ምንም ዓይነት ምግብ እንዳልቀረበላቸው ይገልጻሉ። «ቀኑም ሌሊቱም፣ ጨለማ ነው ለእኛ። ምንግዜም ሌሊቱም ቀኑም ጨልሞብናል፤ መቼ እንደሚነጋ ብቻ ፈጣሪ ብቻ ነው የሚያውቀው። ዝናቡ 24 ሰዓት ነው የሚዘንብብን እንደማንም ብርዱ ይቻል ነበር፤ ግን ረሃብ አይቻልም። »ብለዋል,

እንዲህ ያለ ውጥረት አለመረጋጋቱ በበዛበት በትግራይ ክልል አሁን ላይ በክልሉ ውስጥ የሚኖረው ማኅበረሰብ ከፍተኛ የሆነ ስጋት ውስጥ መሆኑን የሕግ ባለሙያ እና የፖለቲካ ተንታኙ አቶ አወት ይናገራሉ፡፡ የጦርነትን ፈተናን በሚገባ ያውቃል ያሉት ህዝቡ ልዩነቶች በሰላማዊ መንገድ በፈቱ ፍላጎቱ መሆኑም በጉልህ እንደሚታይ እምነታቸውን ገልጸዋል፡፡

ሀብታሞቹ የባሕረ ሰላጤው ሃገራት በቢሊዮን ዶላሮች የሚገመት መዋዕለ-ንዋይ በአፍሪካ በማፍሰስ ላይ ናቸው። የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችና ሳዑዲ አረቢያን የመሳሰሉት ሃገራት የአፍሪካን ገበያ ሲያማትሩ ማሳካት የሚፈልጓቸው አላማዎች ይለያያሉ። ለባሕረ ሰላጤው ሃገራት መዋዕለ-ንዋይ መስፋፋት ገፊው ምክንያት ምንድነው? የአፍሪካ ሃገራትስ ምን ይጠቀማሉ?

የምክክሩ ጉባኤው ታዛቢዎች ከኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ጥምረት፣ ከሙያ ማሕበራት፣ ከኢሰመጉና ከኢሰመኮ የተውጣጡ ናቸው። የጉባኤው ተሳታፊ አንድ የዘርፉ ባለሙያ ከሂደቱ በጎ ውጤት ይጠብቃሉ። ቅድመ ጉባኤው ላይ የጠየቅነው ጥያቄ ምላሽ አላገኘም ያሉ አንድ የሲቪል ድርጅት መሪ በጉባኤው እንዳልተጋበዙ ለዶቼ ቬለ ተናግርዋል።

የቀድሞ የግሬተር ማንቼስተር ከንቲባ የ56 ዓመቱ በርንሀም ትናንት ከበኪንግሀም ቤተ መንግሥት ከተመለሱ በኋላ «ሁሉም ሰው አገሪቱ መሆን ባለባት ቦታ ላይ እንዳልሆነች ሊሰማው ይችላል» ሲሉ ተናግረው ፤የተሻልን መሆን አለብን፣ የተሻልንም እንሆናለን። ተስፋውንም እንመልሳለን» በማለት ለሕዝቡ ቃል ገብተዋል።

በምክክር ሂደቱ ላይ “ዋና ዋና የፖለቲካ ተዋናዮች” በምክክር ሂደቱ ላይ የተቃውሞ እና ገለልተኛ ድምጾች ተሳትፎ እንዲሁም “ህጋዊ የህዝብ ተወካዮች ተሳትፎ” አለመኖሩ ላይ ይስማማሉ ያለው ኦነሰ፤ የመድረኩ አካታችነት እና ገለልተንነት ላይም የሰላ ትችት ነው ያቀረበው፡

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) "ሰላም ማስከበር በሚል ሽፋን የትግራይን ሕዝብ እንደገና ወደ ጦርነት ለመግፋት የሚደረገው አደገኛ አካሄድ መቆም አለበት" በሚል ዛሬ ባወጣው መግለጫ ፣ መንግሥት "ትግራይን እንደገና ወደ አውዳሚ ጦርነት ለመክተት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን" ጠቅሶ ከሷል።
Sponsor detection runs nightly. Check back soon.
No public pitch examples yet for this show.
Generate your own personalised pitchShows with the most semantically similar episode content. Pitch one, pitch all; producers cluster.












DW | Amharic - News has a verified contact on file. Create a free PitchCentric account to access it and generate a personalised pitch in seconds. Research at least 3 recent episodes first and lead with a specific angle that serves their general audience.
DW | Amharic - News is hosted by Unknown Host. The show is categorised under General and has published 13 episodes.
DW | Amharic - News has published 13 episodes.
DW | Amharic - News is accessible for guests with genuine general expertise. A personalised, episode-aware pitch will still outperform a generic one every time.
DW | Amharic - News hasn't explicitly signalled guest openness in recent episodes. That doesn't rule out pitching. your hook just needs to be especially compelling and relevant to their recent content.
Our data rates DW | Amharic - News's guest bar at 80/100 (Premium tier). Established thought leaders with verified media credentials. Sign in to PitchCentric to see how your own Pod Score compares against this show.
Methodology. Booking Probability™ blends Listen Score, 30-day Virality, open-to-guests detection, and Apple ratings. Data refreshed every 60 minutes. Listen Score and Booking Probability are calculated by PitchCentric. Last enriched today.